የMNGD ፕሮጀክት 2022 የአጭር ጊዜ ስልጠና ፕሮግራም አጠናቀው አስሩ ተሳታፊዎች በሰላም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። የዝህ አመት/የዘንድሮው/ ተሳታፊዎች… ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ፍፁም ተስፋዬ፣ ዶ/ር ኤሊያስ አሰፋ፣ ዶ/ር ግርማ ጎንፋ፣ አቶ በላቸው ገብረወልድ፣ አቶ ይታዩ እሸቴ እና አቶ አየነው ይሁኔ ሲሆኑ ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር ኩሴ ጉዲሼ እና ዶ/ር ኢሊያስ […]
Yearly Archives: 2022
ታህሳስ 13፣ 2022 የአጭር ጊዜ ስልጠና መርሃ ግብር የመጨረሻ ቀን በመሆኑ የስልጠና ተሳታፍ ቡድኑ እንደ መጀመሪያው ቀን በኪዮቶ ዩንቨርስቲ ሴሚናር ክፍል ውስጥ በመሰብሰብ የስልጠናውን ማጠቃለያ አውደ ጥናት አካሄዷል። በማጠቃለያ ውይይቱ ላይ ከሚያዛኪ ዩኒቨርሲቲ እና ከኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የMNGD ፕሮጀክት አባላትም በበየነ መረብ ተሳትፈዋል። የማጠቃለያ አውደ ጥናት አቀራረቡ በአራት ቡድን የተከፈለ ሲሆን […]
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኩሴ እና ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤሊያስ ከኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ አካባቢ ጥናት ማዕከል ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ታካሃሺ ጋር በጂንካ ዩኒቨርሲቲ ተገናኝተው፣ በደቡብ ኦሞ የምርምር ማዕከል እና ሙዚየም በተደረጉ ስምምነቶች እንድሁም በኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ አካባቢ ጥናቶች በተመለከተ ተወያይተዋል፡፡
የሥልጠና ተሳታፊዎች ቡድን ከሚስተር ሃጊዋራ ጋር ሐሙስ ታኅሣሥ 8 ቀን ከኢታሚ አየር ማረፊያ ወደ ሚያዛኪ ሲመጡ በሚያዛኪ ዩኒቨርሲቲ የMNGD ፕሮጀክት አባል የሆኑት ዶ/ር ፉኩባያሺ፣ ፕሮፌሰር ካሜይ እና በዩኒቨርሲቲው የMNGD ፕሮጀክት አለም ዓቀፍ ተማሪ አቶ አለምሸት አቀባበል አድርገውላቸዋል። በቀጣዩ ቀን አርብ ዕለት የጂንካ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች የሚያዛኪ […]
የአጭር ጊዜ የሥልጠና ተሳታፊዎች ቡድኑ በታህሳስ 5, 2022. ወደ ኦሳካ ከተጓዙ በኋላ በናካኖሺማ ሚገኘውን የሃንሺን የፍጥነት መንገድን ኩባንያ ዋና መሥሪያ ቤት ከጎበኙ በኃላ በኦሳካ ቤይ የፍጥነት መንገድ በምዕራብ በመመለስ የተቆረጡ ዋሻዎች ግንባታ ቦታዎችን ጎብኝተዋል። ከዚያም በ1995 በታላቁ የሃንሺን የመሬት መንቀጥቀጥ የተበላሹ መዋቅሮችን የሚያሳይ የሃንሺን ኤክስፕረስ ዌይ የመሬት መንቀጥቀጥ ሙዚየም ጎብኝተዋል። […]
የስልጠና ተሳታፊዎቹ በታላቁ ሃንሺን-አዋጂ የመሬት መንቀጥቀጥ ሙዝያም ውስጥ ስለ ድልድዮች ጉዳት እና መንስኤ ተምረዋል። የስልጠና ተሳተፊዎቹ ቪዲዮዎቹን እና ኤግዚቢሽኑን በትኩረት የተመለከቱ እና በጋለ ስሜት ጥያቄዎችን የጠየቁ ሲሆን፤ ከመሬት መንቀጥቀጡ በኋላ ጠፍጣፋ ድልድይ ወደ ትልቅ የተራራ ቅርጽ ተቀይሮ ሲያዩ ፊታቸው ተቀይሮ በላማመን “ትቀልደለህ? በማለት ጠይቀውኛል፡፡ *በዚህ ጉዳይ ላይ የተጻፈ ጽሁፍ እዚሁ […]
የአጭር ጊዜ ስልጠና ተሳታፊዎች ቡድኑ በቀጣይ በኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የምህንድስና ምረቃ ትምህርት ቤት ወደሚገኝበት ወደ ካትሱራ ካምፓስ ሄደው በፕሮፌሰር ኪሺዳ በተሰጠው የጋራ ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ችለዋል። አቶ በላቸው፣ አቶ ይታየው እና አቶ አየነው ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ስራዎቻቸውን/ፕሮጀክቶቻቸውን/ አቅርበዋል። ይህም ለተማሪዎቹ በተለያየ መንገድ የምርምር ፕሮጄክቶች እና ጥናቶቻቸውን የሚያቀርቡበት ትልቅ […]
እ.ኤ.አ. ታህሳስ 2 ቀን 2022 ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጣው የስልጠና ቡድን የሲቪል እና ምድር ሃብቶች ምህንድስና ትምህርት የሚገኝበትን ኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ ካትሱራ ካምፓስን ጎብኝቷል። በጉኝታቸው ወቅትም የMNGD ፕሮጀክት አባል በሆኑት ስለኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና አጭር መግለጫ ከተደረገ በኋላ ቡድኑ የንፋስ ዋሻ ክፍልን (መዋቅራዊ […]
የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች መጀመር በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጠውየነበሩ የMNGD ፕሮጀክት የአጭር ጊዜ የሥልጠና መርሃ ግብሮች ቀጥለዋል። በዚህ ዓመት ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ፤ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሁለት እና ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ ሁለት በድምሩ 10 ተሳታፊዎች በጃፓን ኪዮቶ፣ ኦሳካ እና ሚያዛኪ ዩኒቨርሲቲዎች ለ14 ቀናት ስልጠና ወስደዋል። በስልጠው የሚሳተፈው ቡድን አርብ […]
እ.ኤ.አ ጥቅምት 26 ቀን 2022 ከሰአት በኋላ በጃፓን ኤምባሲ Grassroots Human Security ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ የጃንካ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባውን የሁለገብ አዳራሽ (የማህበረሰብ የመማሪያ ማዕከል/ CLC) የማስመረቅና ለዩኒቨርሲቲው የማስረከብ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል። በርክብክቡ ስነ-ስርዓት ላይ በኢትዮጵያ ከጃፓን ኤምባሲ እና ከጃይካ ኢትዮጵያ ቢሮ ከተውጣጡ ስድስት ሰዎች በተጨማሪ የደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር ተወካዮች የኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ […]
6ኛው የዕድሜ ልክ ሳይንሶች የምርምር ሴሚናር የMNGD የምርምር ሴሚናር ”Challenges and Prospects of Contemporary Paratransit: Mobility, Daily Survival, and Urban Politics in Asia and Africa” በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ ሴሚነሩ የተካሄደበት ቀንና ሰዓት ህዳር 19፣ 2022፣ (ከ9፡00-11፡35 JST/KST(ጃፓን እና ኮሪያ አቆጣጠር)፣ ህዳር 19፣ 2022፣ (ከ8፡00-10፡35 ፒኤችቲ (ፊሊፒንስ አቆጣጠር) ህዳር 18፣ 2022፣ […]
ጥቅምት 26 ቀን 2022 በኢትዮጵያ ከሚገኘው ከጃፓን ኤምባሲ እና ከጃይካ ኢትዮጵያ ጽህፈት ቤት የተውጣጡ ስድስት የስራ ኃላፊዎች በደቡብ ኦሞ ዞን ጂንካ የሚገኘውን የMNGD ፕሮጀክት እንቅስቃሴን ለሁለት ቀናት ጎብኘተተዋል። ጉብኝቱ በጃፓን ኤምባሲ Grant Assistance for Grassroots Human Security Project የገንዘብ ድጋፍ የተገነባውን ሁለገብ የስልጠና እና የትምህርት ማዕከሉን ለጂንካ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ ከማድረግ […]