እ.ኤ.አ. ታህሳስ 2 ቀን 2022 ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና ከጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጣው የስልጠና ቡድን የሲቪል እና ምድር ሃብቶች ምህንድስና ትምህርት የሚገኝበትን ኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ ካትሱራ ካምፓስን ጎብኝቷል።
![](https://mngd.africa.kyoto-u.ac.jp/mngd/wp-content/uploads/2022/12/DSC03698-1024x782.jpg)
በጉኝታቸው ወቅትም የMNGD ፕሮጀክት አባል በሆኑት ስለኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና አጭር መግለጫ ከተደረገ በኋላ ቡድኑ የንፋስ ዋሻ ክፍልን (መዋቅራዊ ምህንድስና ላብራቶሪን) ጎብኝቶ በዶ/ር ኖጉቺ እየተመረ ወደ ሃይድሮሊክ ሜካኒክስ ክፍል አምርቷል። በሃይድሮሊክ ሜካኒክስ ቤተ-ሙከራም በዶ/ር ኦቶዳ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
![](https://mngd.africa.kyoto-u.ac.jp/mngd/wp-content/uploads/2022/12/DSC03730-1024x806.jpg)
![](https://mngd.africa.kyoto-u.ac.jp/mngd/wp-content/uploads/2022/12/DSC03738-751x1024.jpg)
ቡድኑ በመቀጠል የMNGD ፕሮጀክት ሙከራዎች የሚካሄዱበትን የጂኦቴክኒካል ኢንጂነሪንግ ላብራቶሪ ተጎብኝቷል፡፡በዶ/ር ኪዶ እና ከMNGD ፕሮጀክት አለም አቀፍ ተማሪዎች መካከል አንዱ በሆኑት በአቶ ተሾመ አማካይነት ቤተ ሙከራዎች ውስጥ ገለፃ እና ለተነሱትን ጥያቄዎቸ በቂ ምላሽ ተሰጥቷቸው እጆቻቸው ማስታወሻ ለመያዝ እስክደክሙ ድረስ ሲጽፉም ነበር፡፡.
![](https://mngd.africa.kyoto-u.ac.jp/mngd/wp-content/uploads/2022/12/DSC03704-1024x754.jpg)
![](https://mngd.africa.kyoto-u.ac.jp/mngd/wp-content/uploads/2022/12/DSC03711-1024x768.jpg)